ድሆች ለምን ድሃ ሆኑ? የሚለውን ዕድሜ ጠገብ ጥያቄ “ሰነፍ ስለሆኑ፣ የአርባ ቀን ወይም የሰማኒያ ቀን ዕድላቸው ስለሆነ፣ ርግማን ስላለባቸው … ” በማለት በቀላሉ ልንመልስ እንችል ይሆናል። ነገር ግን ድሆች ድሆች የሚሆኑባቸው፣ ድሆችም በመሆኑ የሚቀጥሉባቸው ምክንያቶች ጥልቅ እና ረቂቅ መሆናቸውን ማስተዋል ይጠይቃል። ሰው በተፈጥሮው ድህነትን አይመርጥም ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ያለፍላጎቱ ድህነት በጫንቃው ላይ ሊቀመጥ ይችላል። ለዚህም አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ ከሚችሉት ነገሮች መካከል የመልካም አስተዳደር እጦት፣ አድልዎ፣ አሳሪ ሕጎችና ደንቦች፣ ሙስና፣ ግጭቶችና መፈናቀሎች በዋነኝነት ሊጠቀሱ ይችላሉ። ድሆች ድምጽ አላቸው፤ ነገር ግን ድምጻቸው እምብዛም አይሰማም። ድምጻቸው እንዲሰማ፣ ከመሰማትም አልፎ እንዲያስተጋባ በዙሪያቸው ያሉ ብዙሃን አብረዋቸው ሊጮሁ ይገባል።
ላቭ ዩር ኔበር ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ መሆን አምላካዊ ጥሪ መሆኑን ያምናል። ስለዚህም አማኞች በዙሪያቸው ስላሉ ድሆች በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ድምጻቸውን እንዲያሰሙ፣ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ከራሳቸው ጀምሮ እንዲከላከሉ፣ ለማኅበራዊ ሰላምና ፍትህ በትጋት እንዲሠሩ ያበረታታል፣ የበኩሉንም ድርሻ ይወጣል።
why are the poor, poor? There are some standard responses that we can give to answer this lifelong question. However, there is no simple response. There are many factors which contribute to cause, and the solution is just as complex. No one choses to be poor. However, poor governance, time and chance, complex laws, corruption, conflict, displacement, are front runners is the cause-and-effect category. Disadvantaged communities have a voice, but it is rarely heard. LYN aims to be a voice for these voiceless communities. It will advocate for their rights and hold communities accountable as they exercise their rights and fulfill their responsibilities.
ድሆችን መርዳት ተገቢ ነው። ነገር ግን በተቃራኒው ድሆች ላይ ልናደርስ የምንችለው ትልቁ ጉዳት ሁልጊዜ መርዳት ነው። የተረጂነትና የጥገኝነት አስተሳሰብ ሰዎች ራሳቸውን ለመለወጥ ጥረት እንዳያደርጉ ትልቁ ዕንቅፋት ነው። ይህንን ዕንቅፋት ከመንገድ አስወግዶ በአስከፊ ድህነት ውስጥ የሚኖሩትን ተረጂዎች ወደ አምራችነትና ወደ ረጂነት ለማሻገር ትምህርቶች፣ ሥልጠናዎች እና የመንቀሳቀሻ ድጋፎች ግዙፍ ድርሻ አላቸው።
ላቭ ዩር ኔበር በየአካባቢው ያሉ በአስከፊ ድህነት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች አቅማቸውን ያገናዘበ ትምህርትና ሥልጠና እንዲያገኙ እንዲሁም ለሥራ መንቀሳቀሻ ድጋፎች እንዲመቻቹላቸው በትጋት ይሠራል።
helping is appropriate; however, creating dependency is the risk. LYN will work with its partners to ensure that the right mindset is coupled with the skillsets to lift people out of extreme poverty. This will be done through trainings, and seed funding programs.